Time in Ethiopia:

Showing posts with label World-News. Show all posts
Showing posts with label World-News. Show all posts

Jun 2, 2014

አረብሳት ከኢትዮጵያ የሞገድ አፈና እየተደረገብኝ ነው አለ

Geez Bet | Monday, June 02, 2014
ካቻምናም ታፍኛለሁ፣ ዘንድሮ ግን በህግ እጠይቃለሁ ብሏል
ተቀማጭነቱን በሳዑዲ አረቢያ ያደረገውና በርካታ የቴሌቪዥን ጣቢያዎችን በተለያዩ የዓለም ክፍሎች የሚያሰራጨው የአረብ ሳተላይት ኮሙኒኬሽን ተቋም (አረብሳት) ካለፈው ሳምንት ጀምሮ እየተፈጸመበት ያለው ዓለማቀፍ የሳተላይት ሞገድ አፈና (Jamming) ምንጩ ከኢትዮጵያ መሆኑን እንዳረጋገጠ ገለጸ፡፡

ሳትኒውስ የተባለው የአገሪቱ የዜና ምንጭ ከትናንት በስቲያ እንደዘገበው፣ አረብሳት በሚያስተላልፋቸው በርካታ የቴሌቪዝን ጣቢያዎቹ ላይ መታየት የጀመረውን የስርጭት መስተጓጎል መነሻ ለማወቅ ባደረገው በረቂቅ ቴክኖሎጂ የታገዘ ጥናት፣ ከኢትዮጵያ ግዛት ውስጥ የሚነሳና ሆን ተብሎ የሚፈጸም የሳተላይት ሞገድ አፈና (Jamming) እየተደረገበት መሆኑን ማረጋገጡን አስታውቋል፡፡ ይህን መሰሉ ህገወጥ ድርጊት መፈፀሙ
ሙሉውን አንብብ-Read More

Feb 23, 2014

በተጠለፈው አውሮፕላን ውስጥ የነበረው ኢትዮጵያዊ እማኝነት

Geez Bet | Sunday, February 23, 2014
“የተሳፋሪው ፍላጎት የሆነ መሬት ላይ ማረፍ ብቻ  ነበር”
በሃዋሳ ከተማ በተለምዶ ኬሮ ሰፈር እየተባለ በሚጠራው አካባቢ ተወልዶ ያደገው ወጣት ምህረቱ ገብሬ፣ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በቀድሞው ሀዋሳ ኮምቦኒ የመጀመርያ ደረጃ ት/ቤት ነው የተከታተለው። የሁለተኛ ደረጃ ማጠናቀቂያና የመሰናዶ ትምህርቱንም በቅዱስ ዳንኤል ኮምቦኒ የሁለተኛ ደረጃና የመሰናዶ ት/ቤት አጠናቋል። ከሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ በ2001 ዓ.ም በሲቪል ምህንድስና የመጀመሪያ ዲግሪውን ካገኘ በኋላም፤ እስከ 2004 ዓ.ም ድረስ በዩኒቨርሲቲው ውስጥ በመምህርነት አገልግሏል፡፡ በመቀጠልም ነጻ የትምህርት ዕድል በማግኘት፣ ወደ ጣሊያን አምርቶ የሁለተኛ ዲግሪ ትምህርቱን በመከታተል ላይ ይገኛል፡፡
ሙሉውን አንብብ-Read More

Feb 19, 2014

የጠላፊው ረዳት አብራሪ ጉዳይ አነጋጋሪ ሆኗል

Geez Bet | Wednesday, February 19, 2014
-  መንግሥት ተላልፎ እንዲሰጠው ይፈልጋል:
ባለፈው እሑድ ሌሊት 6፡30 ሰዓት ከአዲስ አበባ ወደ ሮም መብረር የጀመረውን የበረራ ቁጥሩ ‹‹ET 702›› የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቦይንግ 767 አውሮፕላን የጠለፈው ረዳት አብራሪው ኃይለመድኅን አበራ ተገኝ ጉዳይ አነጋጋሪ ሆኗል፡፡
ጠለፋውን ፈጸመ የተባለው ረዳት አብራሪ ቤተሰቦች መሆናቸውን የሚናገሩ፣ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በኃይለመድኅን ላይ ያልተለመዱ ባህሪዎችን መመልከታቸውን ይናገራሉ፡፡
ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ቅርብ የሆኑ ምንጮች ደግሞ ግለሰቡ በተለያዩ ጊዜያት የዲስፒሊን ችግሮች ቢኖሩበትም፣ ብቃት ያለው አብራሪ እንደነበረ ገልጸዋል፡፡
ጉዳዩን በተመለከተ ባለፈው ሰኞ ከቀትር በኋላ መግለጫ የሰጡት የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ሚነስትር አቶ ሬድዋን ሁሴን፣ ግለሰቡ ጠለፋውን ለመፈጸም ምን እንዳነሳሳው እንቆቅልሽ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
‹‹አንድ ሰው በጠለፋ ወንጀል ከተሰማራ ቢያንስ 20 ዓመት ነው የሚፈረድበት፡፡ ከ20 ዓመት በኋላ ምን እንደሚያትርፍ ለጊዜው የታወቀ ነገር የለም፤›› ያሉት ሚኒስትሩ፣ ምን ዓይነት ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች እንደገፉት ለማወቅ ምርመራ መጀመሩን ገልጸዋል፡፡
ረዳት አብራሪ ኃይለመድኅን የ31 ዓመት ወጣት ሲሆን፣ በአየር መንገዱ ለአምስት ዓመታት ያገለገለ መሆኑን የጠቆሙት አቶ ሬድዋን፣ በግለሰቡ የግል ሕይወት ዙሪያ በምርመራ የተደረሰበት መረጃ በአሁኑ ወቅት እንደሌለ ጠቁመዋል፡፡
ሙሉውን አንብብ-Read More

Feb 17, 2014

Co-pilot hijacks plane to Geneva, seeks asylum

Geez Bet | Monday, February 17, 2014
GENEVA (AP) -- An Ethiopian Airlines co-pilot locked his colleague out of the cockpit, hijacked a Rome-bound plane and landed Monday in Geneva, all in an attempt to seek asylum in Switzerland, officials said.
The Boeing 767-300 plane with 202 passengers and crew had taken off from the Ethiopian capital of Addis Ababa and landed in the Swiss city at about 6 a.m. (0500 GMT). Officials said no one on the flight was injured and the hijacker was taken into custody after surrendering to police.
It wasn't immediately clear why the co-pilot, an Ethiopian man born in 1983 whose name wasn't released, wanted asylum. However, Ethiopian Airlines is owned by Ethiopia's government, which has faced persistent
ሙሉውን አንብብ-Read More

Oct 28, 2013