Time in Ethiopia:

Showing posts with label Ethiopia-News. Show all posts
Showing posts with label Ethiopia-News. Show all posts

Dec 24, 2014

Ethiopian pilots very likely to have landed at Eritrea-held Assab Port: source

Geez Bet | Wednesday, December 24, 2014

WASHINGTON, DC - An Ethiopian pilot and two of his crew members defected to Eritrea flying an Mi-35 combat helicopter, the state television announced on Monday.
The pilots were based in the eastern city of Dire Dawa and they executed their plan during what the state-owned TV called a "routine flight training." The announcement came in after days of massive aerial search across northeastern Ethiopia.

The crew members were Captain Samuel Giday, Lt. Bililign Desalegn, and flight technician Tsegaberhan Giday. It was not known whether the pilot and technician are siblings.
The TV didn't specify where in Eritrea the pilot landed the helicopter, but an Ethiopian Air Force source cited the Port of Assab as the most likely place of landing the aircraft.
ሙሉውን አንብብ-Read More

Dec 23, 2014

የሕወሓት አስተዳደር የአስመራው መንግስት ሄሊኮፕተሩን በሱዳን በኩል እንዲመልስለት መጠየቁ ተሰማ

Geez Bet | Tuesday, December 23, 2014
(ምንሊክ ሳልሳዊ) ስርአቱን ከዱ የተባሉት አብራሪዎች ከድሬዳዋ ተነስተው በጅቡቲ ድንበር አስታከው በአሰብ ዘልቀው ኤርትራ ያሳረፉት ሄሊኮፕተር በሱዳን በኩል እንዲመለስለት ሻእቢያን መጠየቁን የሱዳን ዲፕሎማቶች ጠቆሙ::
ወያኔ በኢትዮጵያውያን ላይ የሚያደርገውን ከፍተኛ የሰብአዊ መብት ጥሰት እና በአየር ሃይሉ ውስጥ የሚፈጸመውን ደባ በመቃወም ከድተዋል የተባሉት 2 ፓይለቶች(ካፒቴን ሳሙኤል እና ቢሊሊኝ )እና አንድ ቴክኒሽያን(ጸጋ ብርሃን)ለኤርትራ መንግስት እጃቸውን የሰጡ ሲሆን ይህንንም የወያኔው ቴሌቭዥን ጣቢያ እማኝነቱን ሰቷል::
አብራሪዎቹ ይዘውት የሄዱትን ሄሊኮፕተር እንዲመለስለት ወያኔ የሱዳን ዲፕሎማቶችን የላከ ሲሆን ሻእቢያ የማይመልስ ከሆነ የወያኔ መከላከያ ሰራዊት ከባድ አጸፋዊ እርምጃ እንደሚወስድ አንድ ለስርአቱ ቅርብ የሆነ ድህረገጽ ጽፏል::
በሃገር ውስጥ እና በውጪ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እንደ ፖለቲካ ድል ሲቆጥሩት አንዳንዶቹ ወያኔ የሻእቢያን አየር ሃይል በሰው ሃይል እየገነባ ሊሆን ይችላል ከጀርባ ሌላ ደባዎች በወያኔ እና ሻእቢያ ሊሰራ ይችላል የሚሉ አስተያየት ሰጪዎች አልጠፉም::የወያኔ መክላከያ ሰራዊት አጸፋዊ እርምጃ ይወስዳል የሚል ስጋት ቢያይልም;ሃገር ወዳዶች ግን ምንም እርምጃ አይወስድም የፍርሃት ዛቻ ነው ሲሉ ተደምጠዋል::
ሙሉውን አንብብ-Read More

Ethiopia: Pilot Hijacked Our Military Helicopter to Eritrea

Geez Bet | Tuesday, December 23, 2014
The Ethiopian Defense Ministry charges that a pilot hijacked to Eritrea an attack helicopter which went missing a few days ago.
In a statement issued late Monday the ministry said the pilot of the Ethiopian attack helicopter forced his co-pilot and technician to land in Eritrean territory.
The helicopter was conducting a routine training flight when it disappeared on Friday morning, prompting a massive military search across northern Ethiopia.
It's unusual for Ethiopian army personnel to flee to Eritrea though Eritrean troops often across the border into Ethiopia, citing harsh conditions and forced conscription into the military.
Relations between Eritrea and Ethiopia have been consistently strained since Eritrea gained its independence from the Addis Ababa government in 1993 following a 30-year guerrilla war.

Source: ABC News
ሙሉውን አንብብ-Read More

Jul 1, 2014

10 የሱዳን ወታደሮች በኢትዮጵያ ድንበር አካባቢ ተገደሉ

Geez Bet | Tuesday, July 01, 2014
አፍሪካን ፕሬስ ኤጀንሲ እንደዘገበው 10 የሱዳን ወታደሮች በኢትዮ -ሱዳን ድንበር አካባቢ ከተገደሉ በሁዋላ በድንበር አካባቢ ውጥረት ሰፍሯል። እሁድ እለት ደግሞ ተጨማሪ 13 የሱዳን ወታደሮች መቁሰላቸው የተዘገበ ሲሆን፣ ጥቃቱም በኢትዮጵያ ሚሊሺያዎች ሳይፈጸም እንዳልቀረ ተዘግቧል።
የሱዳን ኮማንዶ ጦር ወደ ኢትዮጵያ ድንበር ሃይሉን እያሰባሰበ መሆኑን የገለጸው ዘገባው፣ በአንድ ወር ውስጥ ለሁለተኛ ጊዜ መካሄዱን ጠቅሷል። ሱዳንና ኢትዮጵያ የድንበር ከተሞቻቸውን ከታጣቂዎች ጥቃት ለመከላከል በሚል  አንዱ በሌላው አገር ድንበር ጥሶ በመግባት እርምጃ እንዲወስድ መስማማታቸው ይታወቃል።
የሱዳን መንግስት ወታደሮቹ መገደላቸውን አምኖ፣ በኢትዮጵያ የመከላከያ ሰራዊት ተገደሉ የሚለውን እንደማይቀበለው አስታውቋል። የሱዳን መንግስት ጦር ቃል አቀባይ ኮሌኔል አልስዋርሚ ካሊድ ሳድ እንደተናገሩት ወታደሮቻቸው የተገደሉት
ሙሉውን አንብብ-Read More

Jun 4, 2014

Ethiopian Man Killed in Atlanta over Gambling

Geez Bet | Wednesday, June 04, 2014
ATLANTA — One man was killed and at least three others wounded in a shooting in Atlanta's historic Auburn Avenue district, authorities said. A fifth person later showed up at Grady Memorial Hospital, and police believe he was also at the scene of the gunfire around 4:30 a.m. Tuesday.

It happened in the street near the intersection of Auburn Avenue and Bell Street, just east of downtown Atlanta.
ሙሉውን አንብብ-Read More

Apr 23, 2014

አርሶ አደሮች መሬታቸውን ያለካሳ እየተነጠቁ ነው

Geez Bet | Wednesday, April 23, 2014
መራዊ፡- በምዕራብ ጎጃም ዞን ሜጫ ወረዳ ያለ ፈቃዳችን መሬታቸውን አሳልፈን አንሰጥም ያሉ አርሶ አደሮች እስርና ድብደባ እየደረሰባቸው መሆኑን ከአካባቢው የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡ በመራዊ አካባቢ ሜጫ ወረዳ እናሸንፋለን ቀበሌ መንግስት
የከርሰ ምድር ውሃ ቁፋሮ እናካሂዳለን በሚል ከ400 በላይ የሚሆኑ አርሶ አደሮች ከመሬታቸው እንዲለቁ የተደረገውን እርምጃ አርሶ አደሮቹ በመቃወማቸው እስርና ድብደባ እየደረሰባቸው መሆኑን የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ጠቁመዋል፡፡ በአካባቢው ከአሁን ቀደም ተመሳሳይ እርምጃዎች የተወሰዱ ሲሆን የአርሶ አደሮቹ መሬት በአበባ ኢንቨስትመንት ላይ ለተሰማሩ ባለሀብቶች ተሰጥቶባቸዋል፡፡ 
         ይህም በአሁኑ ወቅት መንግስት ውሃ ለመቆፈር በሚል አርሶ አደሮቹ ከመሬታቸው እንዲለቁ የሚወስደው እርምጃ በተመሳሳይ  ለአበባ እርሻ ሊሰጥባቸው እንደሆነ በማመናቸው ከመሬታቸው አንለቅም ብለዋል፡፡
ሙሉውን አንብብ-Read More

Mar 10, 2014

ፓትርያርኩ ‹‹ቤተ ክርስቲያን በዩኒቨርስቲ ምሩቃን አትመራም” ማለታቸው ቅሬታ ፈጠረ

Geez Bet | Monday, March 10, 2014
ስለማኅበራት የሰጡትን አስተያየት መልሰው እንዲያጤኑት ተጠየቀ
‹‹ማኅበራት በትኩረት ሊመሩና ጉዟቸውም እየተፈተሸ ሊስተካከል ይገባል›› - መንግሥት
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ‹‹ከዩኒቨርስቲ ተመርቀው ቤተ ክርስቲያንን እንምራ እያሉ ነው፤ ቤተ ክርስቲያኒቱ ትውፊትና ሥርዓት አላት፤እንዲህ ማለት አይችሉም›› በማለት የሰጡትን አስተያየት መልሰው እንዲያጤኑት በንግግራቸው ቅር የተሰኙ የመንፈሳውያን ማኅበራት አገልጋዮች ጠየቁ፡፡
አገልጋዮቹ ለአዲስ አድማስ እንደተናገሩት፣ አቡነ ማትያስ ይሄን አስተያየት የሰነዘሩት በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮ መምሪያ ከኢትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር ጋር በመተባበር የካቲት 21 እና 22 ያዘጋጁት ሀገር አቀፍ የስብከተ ወንጌል የምክክር ጉባኤ በተካሔደበት ወቅት ነው፡፡
ሙሉውን አንብብ-Read More

አንድነት ሁለተኛውን ዙር “የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት”ንቅናቄ ጀመረ

Geez Bet | Monday, March 10, 2014
የመሬት ፖሊስን ለማስለወጥ እታገላለሁ ብሏል
አንድነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ የመሬት ጥያቄን አጀንዳው በማድረግ ለሶስት ወራት የሚዘልቅ ሁለተኛ ዙር “የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት” ንቅናቄ መጀመሩን ጠቁሞ መሬት በመንግስት ቁጥጥር ስር መሆኑን በመቃወም እንደሚንቀሳቀስ ገልጿል፡፡
ፓርቲው በትናንትናው እለት በሠጠው ጋዜጣዊ መግለጫ፤መሬት በመንግስት ቁጥጥር ስር መዋሉን በመቃወም የፖሊሲ ለውጥ እንዲደረግ ጫና ለመፍጠር፣ አዲስ አበባን ጨምሮ በተመረጡ 14 የክልል ከተሞች ህዝባዊ ስብሠባ የሚያካሂድ ሲሆን ስብሠባዎቹ በደሴ እና በድጋሚ በአዲስ አበባ የሚደረግ ሲሆን በየ15 ቀን ልዩነት በሃዋሣ፣ አዳማ፣ ለገጣፎ፣ መቀሌ፣ ደብረታቦር፣ ደብረ ማርቆስ፣ ድሬዳዋ፣ ጂንካ፣ ቁጫ፣ አሶሣ፣ ነቀምት እና ጋምቤላ ከተካሄደ በኋላ አዲስ አበባ ላይ በሚደረግ
ሙሉውን አንብብ-Read More

Feb 26, 2014

<< የፀረ ግብረ ሰዶማዊ ሕጐችን ማውጣት የመንግሥታት ሥራ አይደለም>> ሚኒስትሯ ወይዘሮ ዘነቡ ታደሰ

Geez Bet | Wednesday, February 26, 2014

በሚኒስትሯ የትዊተር ገጽ ላይ የሰፈረው መልዕክት አነጋጋሪ ሆኗል!

-መንግሥት አካውንታቸው ተጠልፏል እያለ ነው::
የሴቶች፣ የሕፃናትና የወጣቶች ጉዳይ ሚኒስትሯ ወይዘሮ ዘነቡ ታደሰ የካቲት 17 ቀን 2006 ዓ.ም. በትዊተር ማኅበራዊ ገጻቸው ላይ፣ ‹‹በተወዳጇ አፍሪካዬ ውስጥ ጥላቻና መገለል ቦታ የላቸውም፡፡
የአለባበስ ሥርዓት ወይም የፀረ ግብረ ሰዶማዊ ሕጐችን ማውጣት የመንግሥታት ሥራ አይደለም፤›› በሚል የወጣው መልዕክት አነጋጋሪ ሆኗል፡፡ መንግሥት ግን የሚኒስትሯ የትዊተር አካውንት መጠለፉን ገልጾ፣ ይህ መልዕክት የሚኒስትሯንም ሆነ የመንግሥትን አቋም አይወክልም ሲል አስተባብሏል፡፡ 

በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ላይ በኡጋንዳ የፀደቀውን ፀረ ግብረ ሰዶማዊያን ሕግ በመቃወም በሚኒስትሯ የትዊተር ገጽ ላይ የተጻፈው ይህ መልዕክት፣ በዓለም ዙሪያ ባሉ የግብረሰዶማዊ መብቶች አቀንቃኞች አድናቆት ተችሮታል፡፡ ሆኖም ግን የሴቶች፣ የሕፃናትና የወጣቶች ጉዳይ ሚኒስቴር የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተሩ አቶ ዓብይ ኤፍሬም፣ ‹‹መልዕክቱ በማይታወቁ ሰዎች የተጻፈ ሲሆን፣ የእሳቸውንም ሆነ የመንግሥትን አቋም የማይገልጽ ነው፤›› ብለዋል፡፡ 
አቶ ዓብይ አክለው፣ ‹‹ሚኒስትሯ ይህን የማኅበረሰብ ሚዲያ የሚጠቀሙት ሕዝቡ በቀጥታ ሊያገኛቸው የሚገቡ መልዕክቶችን ለማስተላለፍ አዋጭ ሚዲያ በመሆኑ ነው፤›› ብለዋል፡፡ የትዊተር ገጻቸውን የሚያንቀሳቅሱት ራሳቸው ወይዘሮ ዘነቡ መሆናቸውን የገለጹት አቶ ዓብይ፣ በገጻቸው ላይ በጠላፊዎች በተላለፈው መልዕክት ሚኒስትሯ ማዘናቸውን አስረድተዋል፡፡ 
የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ ሽመልስ ከማል የሚኒስትሯ የትዊተር አካውንት መጠለፉን አረጋግጠው፣ ‹‹የሚኒስትሯን አካውንት ጠልፈው በመግባት የእሳቸውንና የመንግሥትን አቋም የማይገልጽ
ሙሉውን አንብብ-Read More

በኑሮ መማረሩን ተናግሯል የተባለው የጥበቃ አባል ራሱን አጠፋ

Geez Bet | Wednesday, February 26, 2014
በቦሌ ዋናው መንገድ ከሚሊኒየም አዳራሸ ማዶ በሚገኘው የሕብረት ባንክ አክሲዮን ማኅበር ቅርንጫፍ በጥበቃ ሥራ ላይ የተሰማራው ወጣት፣ ‹‹ኑሮ መሮኛል›› በማለት እየተናገረ ለጥበቃ በያዘው ጠመንጃ የካቲት 17 ቀን 2006 ዓ.ም. ከሰዓት በኋላ ራሱን አጠፋ፡፡
ወጣቱ የጥበቃ ሠራተኛ በሱፈቃድ በጋሻው በኪሱ ውስጥ ከተገኙት የተለያዩ መታወቂያዎች መረዳት እንደተቻለው፣ አጋር የጥበቃ ሠራተኞች ማሠልጠኛ ተቋም ተቀጣሪ ነው፡፡ በተጨማሪም የኮሌጅ ተማሪ መሆኑን በሚገልጸው መታወቂያ ላይ እንደሠፈረው ከሆነ፣ በ1982 ዓ.ም. የተወለደና የ24 ዓመት ወጣት ነው፡፡ በምን ምክንያት ከፖሊስ ባልደረባነት እንደለቀቀ ባይታወቅም፣ የ13ኛ ኮርስ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አባል እንደነበር በቅርብ ከሚያውቁት ወዳጆቹ ለማወቅ ተችሏል፡፡
በባንኩ አሠራር አንድ የጥበቃ አባል 24 ሰዓት ሠርቶ 24 ሰዓታት የሚያርፍ በመሆኑ፣ ሟች በሱፈቃድም የካቲት 17 ቀን 2006 ዓ.ም. ጠዋት አዳሪ ጓደኛውን ከቀየረ በኋላ፣ ባንኩን ለመጠበቅ የቻለው ለ24 ሰዓታት ሳይሆን ለሰባት ሰዓታት ብቻ ነው፡፡ ወጣቱ ‹‹ኑሮ መሮኛል›› በማለት እያማረረ እያለ በመሀል የያዘውን ጠመንጃ ቃታ በመሳብ አንድ ጊዜ ወደ ላይ ሲተኩስ፣ አብረውት የነበሩ ሴት ፈታሽና ሌሎች የባንኩ ተጠቃሚዎች በመደናገጥ ወደ ውስጥና ወደ ውጭ ሽሽት ይጀምራሉ፡፡ ሁለተኛውን ጥይት በመተኮስ ወደ ሚሊኒየም አዳራሽ በኩል በፍጥነት መራመድ መቀጠሉን በሥፍራው የነበሩ የዓይን እማኞች ተናግረዋል፡፡ 
ሦስተኛውን ጥይት ወደ ላይ ከተኮሰ በኋላ አራተኛውን አንገቱ
ሙሉውን አንብብ-Read More

የሱዳን ወዳጅነት ከጉርብትናም በላይ?

Geez Bet | Wednesday, February 26, 2014
ጠቅላይ ሚኒስቴር መለስ ዜናዊ በእያንዳንዱ የሕወሓት የልደት በዓል ማለትም የካቲት 11 በዋነኝነት ከሚከበርበት የትግራይ ርዕሰ ከተማ መቐለ ተገኝተው በሚያደርጉት ንግግር በዓሉን ሁሌም ድምቀት ይሰጡት ነበር፡፡
ሥልጣን ላይ ያለው ኢሕአዴግ ዋነኛ መሥራች የሆነውን ሕወሓት የረጅም ጊዜ ጠንካራ ሊቀመንበሩን ያጣው ባለፈው ዓመት በዓሉን ከማክበሩ ስድስት ወራት በፊት ነበር፡፡
አቶ መለስ ለመጀመርያ ጊዜ ያልተገኙበት 38ኛው በዓል ግን እሳቸውን በመዘከር በሐዘን ድባብ ነበር ያለፈው፡፡ ተተኪያቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝም በወቅቱ በበዓሉ ላይ ቢገኙም፣ በአቶ መለስ መሪነት እዚህ ደርሷል ያሉት ሥርዓት ከፍተኛውን መስዋዕትነት ከፍሎበታል ካሉት ከትግራይ ሕዝብ ጋር እጅና ጓንት በመሆን እንደሚሠሩ፣ ‹‹የማፅናኛ›› ንግግር አድርገው ነበር የተመለሱት፡፡ 
ዘንድሮ የተከበረው 39ኛው የሕወሓት በዓል ግን ባለፈው ዓመት በሐዘን ድባብ ያለፈውን በዓል ያካካሰ በሚመስል ሁኔታ እጅግ ደማቅ ነበር፡፡ በኢትዮጵያ ላለፉት 22 ዓመታት ሥልጣን ላይ የቆየው ኢሕአዴግ ዋነኛ አካል የሆነው ሕወሓት፣ በሚቀጥለው አርባኛ የልደት ዓመቱ በበለጠ በደመቀ ሁኔታ ያከብራል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ የዘንድሮው ግን ከተገመተው በላይ ደማቅ ሆኖ ተከብሯል፡፡ 
የሕወሓት በዓል እጅግ እንዲደምቅ ምክንያት የሆነው ባለፉት ሁለት ዓመታት የተለየ የሠራው ነገር ኖሮ አይመስልም፡፡ እንዲያውም ድርጅቱ ጠንካራ መሪውን በሞት ካጣ በኋላ መረጋጋት ተስኖት በውስጥ መከፋፈልና እርስ በርስ በመወነጃጀል ማሳለፉ ይነገራል፡፡ የድርጅቱ ሌሎች አንጋፋ መሪዎችም ያላግባብ ከአመራር መሸኘቱ ከፍተኛ ትችት ያስተናገደበት ዓመት ነበር፡፡ በሌሎች ዓመታት እንደተለመደው
ሙሉውን አንብብ-Read More

Feb 20, 2014

መሬትና ዉሃ ቅርምት በኢትዮጵያ

Geez Bet | Thursday, February 20, 2014
ኢትዮጵያ ዉስጥ የመሬትና ዉሃ ቅርምት ማኅበረሰቡን እየጎዳ እንደሚገኝ ዓለም ዓቀፉ የመብት ተሟጋች ሂዉማን ራይትስ ዎች አመለከተ። ድርጅቱ ይህን አመልክቶ ባወጣዉ ዘገባ በዚህ ምክንያትም ኢትዮጵያና ኬንያ ዉስጥ 500,000 አርብቶ አደሮች ለችግር መጋለጣቸዉን ገልጿል። 
ሂዉማን ራይትስ ዎች፤ ኢትዮጵያ፤ የመሬትና ዉሃ ቅርምት ማኅበረሰቦችን ጎዳ በሚል ዛሬ ባወጣዉ ዘገባ፤ አዳዲስ ከሳተላይት የተገኙ ምስሎች በታችኛዉ ኦሞ ሸለቆ አካባቢ ነባር ማኅበረሰቦች ይጠቀሙበት የነበረዉን መሬት ለስኳር ልማት በስፋት መመንጠሩን ማሳየታቸዉን አመልክቷል። ላለፉት አምስት ወራትም 7,000 የሚሆኑ የቦዲ ጎሳ አባላት ጋ በቂ ምክክር ሳይደረግ ተግባሩ መከናወኑን ዘርዝሯል። የድርጅቱ የአፍሪቃ ጉዳይ ምክትል ዳይሬክተር ሌስሊ ሌፍኮ፤ ድርጅታቸዉ በUNESCO በዓለም ቅርስነት
ሙሉውን አንብብ-Read More

Feb 19, 2014

የጠላፊው ረዳት አብራሪ ጉዳይ አነጋጋሪ ሆኗል

Geez Bet | Wednesday, February 19, 2014
-  መንግሥት ተላልፎ እንዲሰጠው ይፈልጋል:
ባለፈው እሑድ ሌሊት 6፡30 ሰዓት ከአዲስ አበባ ወደ ሮም መብረር የጀመረውን የበረራ ቁጥሩ ‹‹ET 702›› የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቦይንግ 767 አውሮፕላን የጠለፈው ረዳት አብራሪው ኃይለመድኅን አበራ ተገኝ ጉዳይ አነጋጋሪ ሆኗል፡፡
ጠለፋውን ፈጸመ የተባለው ረዳት አብራሪ ቤተሰቦች መሆናቸውን የሚናገሩ፣ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በኃይለመድኅን ላይ ያልተለመዱ ባህሪዎችን መመልከታቸውን ይናገራሉ፡፡
ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ቅርብ የሆኑ ምንጮች ደግሞ ግለሰቡ በተለያዩ ጊዜያት የዲስፒሊን ችግሮች ቢኖሩበትም፣ ብቃት ያለው አብራሪ እንደነበረ ገልጸዋል፡፡
ጉዳዩን በተመለከተ ባለፈው ሰኞ ከቀትር በኋላ መግለጫ የሰጡት የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ሚነስትር አቶ ሬድዋን ሁሴን፣ ግለሰቡ ጠለፋውን ለመፈጸም ምን እንዳነሳሳው እንቆቅልሽ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
‹‹አንድ ሰው በጠለፋ ወንጀል ከተሰማራ ቢያንስ 20 ዓመት ነው የሚፈረድበት፡፡ ከ20 ዓመት በኋላ ምን እንደሚያትርፍ ለጊዜው የታወቀ ነገር የለም፤›› ያሉት ሚኒስትሩ፣ ምን ዓይነት ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች እንደገፉት ለማወቅ ምርመራ መጀመሩን ገልጸዋል፡፡
ረዳት አብራሪ ኃይለመድኅን የ31 ዓመት ወጣት ሲሆን፣ በአየር መንገዱ ለአምስት ዓመታት ያገለገለ መሆኑን የጠቆሙት አቶ ሬድዋን፣ በግለሰቡ የግል ሕይወት ዙሪያ በምርመራ የተደረሰበት መረጃ በአሁኑ ወቅት እንደሌለ ጠቁመዋል፡፡
ሙሉውን አንብብ-Read More

Feb 17, 2014

Co-pilot hijacks plane to Geneva, seeks asylum

Geez Bet | Monday, February 17, 2014
GENEVA (AP) -- An Ethiopian Airlines co-pilot locked his colleague out of the cockpit, hijacked a Rome-bound plane and landed Monday in Geneva, all in an attempt to seek asylum in Switzerland, officials said.
The Boeing 767-300 plane with 202 passengers and crew had taken off from the Ethiopian capital of Addis Ababa and landed in the Swiss city at about 6 a.m. (0500 GMT). Officials said no one on the flight was injured and the hijacker was taken into custody after surrendering to police.
It wasn't immediately clear why the co-pilot, an Ethiopian man born in 1983 whose name wasn't released, wanted asylum. However, Ethiopian Airlines is owned by Ethiopia's government, which has faced persistent
ሙሉውን አንብብ-Read More

Feb 15, 2014

የባህርዳር ዩኒቨርስቲ ሠራተኞች በአስተዳደራዊ ችግር ተማረናል አሉ

Geez Bet | Saturday, February 15, 2014
“የግንዛቤ ችግር ያለባቸው ሰራተኞች አሉባልታ ነው” - ዩኒቨርስቲው

በባህርዳር ዩኒቨርስቲ አስተዳደራዊ ችግር መማረራቸውን የተናገሩት የዩኒቨርስቲው ሠራተኞች፤በየጊዜው  መምህራን ሥራቸውን እየለቀቁ እንደሚወጡ ገለፁ፡፡ የዩኒቨርስቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ባይሌ ዳምጤ በበኩላቸው፤ የግንዛቤ ችግር ያለባቸው ሰራተኞች አሉባልታ እንጂ በዩኒቨርስቲው ውስጥ አስተዳደራዊ ችግር እንደሌለ  ለአዲስ አድማስ ተናግረዋል፡፡
በዓመት ከ1.2 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት የሚመደብለት፣ ከ45 ሺህ በላይ ተማሪዎች የሚያስተምርና ከአምስት ሺህ በላይ ሰራተኞች የሚያስተዳድረው ዩኒቨርስቲው፤ ከአመራርና አስተዳደር ሙያ ጋር የተገናኘ የትምህርት ዝግጅት በሌላቸው አመራሮች እየተመራ፣ ለከፍተኛ አስተዳደራዊ ችግር መጋለጡን ቅሬታ አቅራቢዎቹ ገልፀዋል፡፡
 አንድ የዩኒቨርስቲው ሠራተኛ በሰጠው አስተያየት፤ የዩኒቨርስቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር ባይሌ ዳምጤ በፊዚክስ፣ምክትሉ ዶ/ር ፍሬው አሞኜ በእንስሳት ህክምና፣ሌላው ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር እያዩ  በባዮሎጂ የተመረቁ መሆናቸውን በመጠቆም፣ አንዳቸውም በአስተዳደር ወይም በአመራር ሙያ አለመመረቃቸውን አስረድቷል፡፡ “አመራሩ ለምን በተፈጥሮ ሳይንስ ምሁራን በሞኖፖል እንደተያዘ አልገባኝም” ብሏል፡፡ የፕሬዚዳንትና የምክትል ፕሬዚዳንቶቹ እርስ በእርስ አለመግባባትና በየስብሰባው መዘላለፍ ሌላው የአስተዳደሩን ችግር ያባባሰ ጉዳይ መሆኑን የሚገልፁት ቅሬታ አቅራቢዎች፤ የአመራሮቹ ውዝግብ በተቀረው ሰራተኛ ላይ ተፅዕኖ ማሳደሩን አልሸሸጉም፡፡
ዩኒቨርስቲው ከ159 ሚሊዮን ብር በላይ አውጥቶ ከከተማው ማዘጋጃ ቤት ለመምህራን ኮንዶሚኒየም ቤቶች ቢገዛም እስካሁን  ለመምህራኑ አላስረከበም ሲሉ የሚወቅሱት ሠራተኞቹ ፤ህንፃዎቹ ያለ አገልግሎት ቆመው እየተሰነጣጠቁና ለመፀዳጃነት እየዋሉ እንደሆነ ጠቅሰው፤ ዩኒቨርስቲው እስካሁን ወደ 20 ሚሊዮን ብር መክሰሩንና ህንፃዎቹን ለማደስ ከ20 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ እንደሚጠብቀው ተናግረዋል፡፡
የዩኒቨርስቲው አመራር፣ የመምህራርንንም ሆነ የሌሎች ሠራተኞችን ቅሬታ ለመስማትና መፍትሄ ለማበጀት ዝግጁ አይደለም የሚሉት ቅሬታ አቅራቢዎቹ፤ በዚህም የተነሳ በተለይ ወጣቶችና ትዳር ያልያዙ መምህራን በአስተዳደራዊ ችግር እየተማረሩ በየጊዜው ሥራቸውን እየለቀቁ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ የዩኒቨርስቲው ሁለት ምክትል ዲኖችም ከመማረራቸው የተነሳ የአገልግሎት ክፍያ ሳያገኙ ሥራቸውን ጥለው እንደወጡ ገልፀዋል፡፡
የዩኒቨርስቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ባይሌ ዳምጤ በበኩላቸው፤ ሠራተኞች የሚለቁት የተሻለ ደሞዝ ሲያገኙ እንጂ በአስተዳደራዊ ችግር እንዳልሆነ ይናገራሉ፡፡ አስተዳደራዊ ችግር እንዳለ የሚያወሩት የግንዛቤ ችግር ያለባቸው ሰራተኞች እንደሆኑም ገልፀዋል - ፕሬዚዳንቱ፡፡ ባህርዳር ዩኒቨርስቲ በአገር ውስጥ ካሉት ምርጥ ዩኒቨርስቲዎች ከሦስተኛ እስከ አምስተኛ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ የገለፁት ዶ/ር ባይሌ፤  የተለያዩ መሥሪያ ቤቶች በቀጥታ ከዩኒቨርስቲው በርካታ ምሩቃንን እንደሚቀጥሩ ተናግረዋል፡፡ የዩኒቨርስቲው አመራር የትምህርት ዝግጅት፣ ከአስተዳደር ሙያ  ጋር ስለማይገናኝ ዘርፈ ብዙ አስተዳደራዊ ችግሮች እየተፈጠሩ ነው በሚል የተነሱ ቅሬታዎችንም ፕሬዚዳንቱ አይቀበሉትም። “ማንኛውም ሰው የመጀመርያ ድግሪውን በየትኛውም ዘርፍ ሊሰራ ይችላል፤ ለምሳሌ የአገሪቱ ጠ/ሚኒስትር የመጀመርያ ድግሪ ከአመራር ጋር የተገናኘ አይደለም” ያሉት ዶ/ር ባይሌ፤ አንድ ሰው ተመራማሪ መሆኑ ከአመራርነት አያግደውም ሲሉ ተሟግተዋል፡፡ እኔ የፊዚክስ ሰው ስለሆንኩ መምራት አልችልም ማለት አይደለም ያሉት ዶ/ሩ፤ ይሄ የሚያሳየው የቅሬታ አቅራቢዎቹን አላዋቂነት ብቻ ነው ብለዋል፡፡ የፕሬዚዳንቶቹን አለመግባባትና መዘላለፍ በተመለከተ ሲያስረዱም ፤ በሃሳብ አለመግባባትና የሃሳብ ልዩነትን እንደተራ ጠብ ማየት የግንዛቤ ችግር ነው ያሉት ፕሬዚዳንቱ፣ዋናው ለአላማ መሥራት እንጂ የሰዎች ግንኙነት መሆን የለበትም  ብለዋል፡፡  
ከከተማው ማዘጋጃ ቤት ለመምህራን የተገዙትን ቤቶች በተመለከተ ሲመልሱም “ዩኒቨርስቲው ቤት ለመግዛት ብር ከፈለ እንጂ ቤት አይገነባም” ያሉት ፕሬዚዳንቱ፤ መረጃ ሰጪዎቹ ያለ እውቀት ወሬ ይዘው የሚሮጡ በመሆናቸው ነው እንጂ ችግሩ የተከሰተው በቤቶች ልማት አቅም ማነስ እንደሆነ ተረጋግጦ፣ ዩኒቨርስቲው የቤቶቹን የማጠናቀቂያ  ሥራ ለመሥራት ውሳኔ ላይ ደርሷል ብለዋል፡፡
ከጥቂት ወራት በፊት ዩኒቨርስቲው የገዛውን ይሄንኑ ኮንዶሚኒየም ለመምህራኑ ሳያስረክብ በመቅረቱ  ዩኒቨርስቲው ለ20 ሚሊዮን ብር ኪሳራ መዳረጉን መዘገባችን ይታወሳል፡፡
Source: addis Admass
 
ሙሉውን አንብብ-Read More

Feb 5, 2014

የሐሮማያ ዩኒቨርሲቲ አመራሮችና ተማሪዎች ተጋጩ

Geez Bet | Wednesday, February 05, 2014
በሐሮማያ ዩኒቨርሲቲ የኢንቫይሮመንታል ኢንጂነሪንግ ተማሪዎች ‹‹ኢንቫይሮመንትን በሚመለከት የምንማረው ትምህርት ስለሌለ ካሪኩለሙ ተቀይሮ ኃይድሮሊክ ኢንጂነሪንግ በሚል ይቀየርልን›› በማለት ከጥር 23 ቀን 2006 ዓ.ም. ጀምሮ ከዩኒቨርሲቲው አመራሮችና የፖሊስ ሠራዊት ጋር መጋጨታቸውን፣ በሥፍራው የተገኙ የዓይን እማኞች ለሪፖርተር ገለጹ፡፡ 

ዩኒቨርሲቲው ፈንድ ስለሚያገኝበት ብቻ ኢንቫይሮንመንታል ኢንጂነሪንግ በሚል ስያሜ የማይማሩትን ትምህርት እንደተማሩ በማስመሰል ዲግሪ የሚሰጣቸው ከሆነ፣ በማይታወቅና ምንም ጥቅም በሌለው የትምህርት መስክ ከመቀመጥ ባለፈ ሌላ ጥቅም እንደማያገኙበት በመግለጽ፣ ካሪኩለሙ እንዲቀየር አጥብቀው መጠየቃቸውን ሪፖርተር ያጋገራቸው አንዳንድ ተማሪዎች አስረድተዋል፡፡ 
ሙሉውን አንብብ-Read More

የእግር ኳሱን አንኳር ችግር መንካት የተሳነው ግምገማ

Geez Bet | Wednesday, February 05, 2014
ክስተቱ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በጥሩም በመጥፎም እያነጋገረ ሰንብቷል፡፡ ከሁለት ዓመት በፊት አንዳንዶች ‹‹በአጋጣሚ›› አንዳንዶች ደግሞ ‹‹በጥረት›› በሚሉት መንገድ ወደ አፍሪካ ዋንጫ፣
እንዲያም ሲል ለዓለም ዋንጫ ማጣርያ ከአሥር የአፍሪካ ምርጦች አንዱ ሆኖ የመጣው የዋሊያዎቹ ቡድን፣ እንደ አመጣጡ መጓዝ ተስኖት የተሰናበተ የቻን የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ትዝብት ውስጥ ጥሎታል፡፡

አንድም ጐል ሳያስቆጥር በሁሉም ግጥሚያዎች ተሸንፎ ከውድድሩ ውጭ መሆኑ ብዙ አስነቅፎታል፡፡ ከሕዝቡ የተሰነዘረበት ትችት የበረታ መሆኑን ተከትሎ ተጨዋቾቹ፣ አሰልጣኙና ሌሎችም በቡድኑ ውስጥ ኃላፊነት ያላቸው አካላት ቅሬታቸውን ሲያሰሙ
ሙሉውን አንብብ-Read More

Feb 4, 2014

የቀድሞ የጋምቤላ ክልል ፕሬዚዳንት ከአገር ኮበለሉ

Geez Bet | Tuesday, February 04, 2014
የቀድሞው የጋምቤላ ክልል ፕሬዚዳንት የነበሩትና በአሁኑ ሰዓት የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስትር ዴኤታ የሆኑት የተከበሩ አቶ ኡመድ ኡባንግ፤ ከአገር መኮብለላቸውን ምንጮቻችን ገለፁ፡፡ አቶ ኡመድ ኡባንግ ባለፈው ሳምንት መጀመሪያ ላይ ከሃገር መውጣታቸውን የጠቆሙት ምንጮች፤ ወደ ኢትዮጵያ እንደማይመለሱ ለሚቀርቧቸው ሰዎች መናገራቸውን አመልክተዋል።
የሚኒስትር ዴኤታውን መኮብለል በተመለከተ የጠየቅናቸው የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስትር ዶ/ር ሽፈራው ተክለማርያም፤ አቶ ኡመድ በስራ ገበታቸው ላይ እንደሌሉ ማረጋገጣቸውን
ሙሉውን አንብብ-Read More

Jan 27, 2014

ባሏ በነዳጅ ያቃጠላት እናት ሞተች

Geez Bet | Monday, January 27, 2014
በአዲስ አበባ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፤ ባሏ በነዳጅ ቃጠሎ ያደረሰባት ወ/ሮ ብዙነሽ ነጋ ከአራት ሳምንት ስቃይ በኋላ ማክሰኞ እለት የሞተች ሲሆን፤ ድርጊቱን ፈጽሟል የተባለው አቶ ሽታው ሁሴን በፖሊስ ተይዞ ምርመራ እየተካሄደ ነው፡፡
ለ12 አመታት በትዳር የቆዩት ባልና ሚስት አንድ ልጅ ማፍራታቸውን የገለፁት ዘመዶች እንደሚሉት፤ በሟቿ ላይ የደረሰው ጥቃት ያልታሰበ ዱብዕዳ አይደለም፡፡ ለበርካታ ጊዜ ባለትዳሮቹ እየተጋጩ፤ ወ/ሮ ብዙነሽ በተደጋጋሚ ጥቃት ይደርስባት ነበር ብለዋል፡፡
አቶ ሽታው ባለቤቱን ከቤተሰብና ከጐረቤት ጋር እንዳትቀራረብ ብቻ ሳይሆን ከቤት ውጭ እንዳትንቀሳቀስ እያስፈራራ፣ በተደጋጋሚ ጉዳት እንዳደረሰባት የሚናገሩት የሟች እህት ወ/ሮ አበባ ነጋ፤ ባለፈው ወር ታህሳስ 17 ቀን እኔ ቤት ቆይታ አመሻሽ ላይ ወደ ቤቷ ከሄደች በኋላ ነው
ሙሉውን አንብብ-Read More

ሂውማን ራይትስ ዎች በኢትዮጵያ የፖለቲካ ምህዳሩ ይበልጥ ጠቧል አለ

Geez Bet | Monday, January 27, 2014
መንግስት፤ ተቋሙ የተቃዋሚዎች የፕሮፖጋንዳ ማስፈፀሚያ ነው
“በኢትዮጵያ የነፃ ሚዲያ ህልውና አደጋ ላይ ነው”
“በኤርትራ የመብት ጥያቄ ማንሳት ነውር ሆኗል” ብሏል

የኢትዮጵያ መንግስት የዜጐችን  ሰብአዊ መብት በስፋት ይጥሳል በማለት ተደጋጋሚ ወቀሳና ስሞታ የሚያቀርበው ሂውማን ራይትስ ዎች የተሰኘው አለማቀፍ የመብት ተቋም፤  ሰሞኑን ይፋ ባደረገው አመታዊ ሪፖርቱ፣ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ነፃነት ይበልጥ መጥበቡንና የነጻ ሚዲያ ህልውና አደጋ ላይ መውደቁን ገለፀ፡፡
የኢትዮጵያ መንግስት በበኩሉ፤ የተቋሙን ሪፖርት ያጣጥላል፡፡ በአገሪቱ ውስጥ የፖለቲካ ነፃነትና የፖለቲካ እንቅስቃሴ የማካሄድ እድል (የፖለቲካ ምህዳር) እየጠበበ የመጣው ከምርጫ 97 በኋላ መሆኑን የገለፀው ሂውማን ራይትስ ዎች፤ ከዚያ ወዲህ በመንግስት የፀደቁትን የፀረ - ሽብር እና የበጐ አድራጐት ማህበራት አዋጆችን በምሳሌነት ጠቅሷል፡፡
ሙሉውን አንብብ-Read More